ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲሱ ስፖንሰሬ አሲክስ @asics ብራንድ በመሮጥ በፒችትሪ 10ኪ.ሜ 27:49 የራሴን ፈጣን ሰዓት በመሮጥ 3ተኛ በመውጣቴ በጣም ደስ ብሎኛል። ወደፊት ከ አሲክስ ጋር ለበለጠ ስኬት ተዘጋጅቻለሁ። በርግጥ ናይክን በጣም አመሰግናለሁ ላለፉት ስድስት አመታት አብሮኝ በመሆን የአለም ዋንጫ፣ የአለም ክሮስ ካንትሪ፣ የአለም ግማሽ ማራቶን እና ሶስት የአፍሪካ ሻምፒዮና ተሳታፊ እንድሆን አግዞኛል። በተለይ የሆስተን ግማሽ ማራቶን ያሸነፍኩበት፣ ቫሌንሽያ ግማሽ ማራቶን የኢትዮጵያ ሬኮርድ የያዝኩበት እና ቦስተን ማራቶን 3ተኛ የወጣሁበት የጎዳና ስኬቶቼ ለኔ ልዩ ናቸው።
ለበለጠ ስኬት አሁንም እንደዎትሮው ከቡድን አጋሮቼ፣ ከአሰልጣኜ ፣ ከማኔጅመንቴ እና አሲክስ ጋር ጠንክሬ ሰራላሁ።
📷 Paul Ward / @atlantatrackclub